ለተቋሙ ሴት አሰልጣኞችና ባለሙያዎች የአመራርነት ስልጠና ተሰጠ።
የካቲት 22/2016 ዓ ም
በስልጠናው መጀመሪያ ላይ የተገኙት የEASTRIP ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ አብርሃም ለገሰ እንደተናገሩት የተቋሙን ሴቶች ለአመራርነት ብቁ ለማድረግ ታስቦ የሚሰጥ ስልጠና በመሆኑ በቀጣይ አራት ቀናት በተለያዩ ዕርሶችና በተለያዩ አሰልጣኞች የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ ሴት ባለሙያዎችን ብቻ ያሳተፈው ስልጠና በዓይነቱ የመጀመሪያ እንደሆነና ቀጣይነት እንደሚኖረውም አቶ አብርሃም ጠቁመዋል።
የዛሬውን ስልጠና የሰጡት ከሲቪል ሰርቪስ ዩንቨርስቲ አሰልጣኝ ወ/ሮ ኤደን ቡሽራ ሲሆኑ ስለ አመራርነት ምንነትና ሴቶች እንዴት ወደ አመራርነት መምጣት የሚችሉባቸውን መንገዶች አብራርተዋል።
ትክክለኛ የኢንስቲትቱን መረጃዎችን ለማግኘት የኢንስቲትዩቱን
ፌስቡክ ገጽ https://www.facebook.com/tticommunication ወይም
ቴልግራም https://t.me/tticommunication
ዌብሳይት https://www.tti.edu.et/ ይጎብኙ

Recent Comments