ፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት
Federal Tourism Training Institute
We Strive for Excellence

በንብረት አስተዳደርና አወጋገድ እንዲሁም ኢ ፍሊት ማኔጅመንት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ

March 17, 2026
በንብረት አስተዳደርና  አወጋገድ እንዲሁም  ኢ ፍሊት ማኔጅመንት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ

ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ከፌዴራል የመንግስት ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን ጋር በመተባበር ስለ መንግስት ንብረት አስተዳደር እና አወጋገድ እንዲሁም e- Fleet ማንጅሜንት ለሚመለከታቸው የሥራ ክፍል ኃላፊዎችና ሠራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል።
ስልጠናውን ያስጀመሩት የተቋሙ የሥራ አመራርና አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ አባተ የመንግስት የንብረት አስተዳደር ፣ እንዲሁም አወጋገድ እና (e-Fleet Management) የመኪኖች ስምሪት ፣ ለጥገናና ነዳጅ አጠያየቅ ስልጠና መውሰዱ በኤሌክትሮኒክስ ሲስተም ተጠቅሞ አሰራርን ማዘመን ጊዜን፣ ሀብትን እንዲሁም ጉልበትን የሚቆጥብ በመሆኑን በአግባቡ መከታተል እንደሚገባ አሳስበዋል።
ኢንስቲትዩቱ ከስልጠናው በኋላ የንብረት አወጋገድን ፣ የመኪና ስምሪት፣ ጥገናና ነዳጅ ጥየቃ ወደ ሲስተም እንደሚገባም ተገልጿል።
ስልጠናውን የሰጡት ከፌዴራል መንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ባለሥልጣን አቶ ደበበ ማሞ እና አቶ ኃይለሚካኤል ብሩ ናቸው።

Gallery image
Gallery image