የኢንስቲትዩቱ ሰልጣኞች ትምህርታዊ ጉብኝት አደረጉ

May 28, 2026
የኢንስቲትዩቱ  ሰልጣኞች ትምህርታዊ ጉብኝት አደረጉ

ቱ.ማ.ኢ ግንቦት 18/2018 ዓ.ም
የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት የቱሪዝም ትምህርት ክፍል ሰልጣኞች በአዲስ አበባ የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎች ትምህርታዊ ጉብኝት አድርገዋል።
በዚህ ጉብኝት የአዲአበባ ዩንቨርሲቲ የእንስሳት ተፈጥሮ ቅርስ ጥበቃ መዘክር፣ የአድዋ ድል መታሰቢያ፣ የጉለሌ እጽዋት እና የእንጦጦ ፓርክ ተጎብኝቷል።
በጉብኝቱ የቱሪዝም ማኔጀመንት ሦስተኛ ዓመት፣ የቱርጋይድና የቱር ኦፕሬሽን አንደኛ እና ሁለተኛ ዓመት ሰልጣኞች በትምህርታዊ ጉብኝቱ እየተሳተፉ እንደሆኑ የቱሪዝም ፋካሊቲ ዲን አቶ ሲሳይ አብርሃም ተናግረዋል።
በዚህ ትምህርታዊ ጉብኝት የተሳተፉ ሰልጣኞች እንደተናገሩት ጉብኝቱ በንድፈ ያገኘነውን ዕውቀት በተግባር እንድናየው እድል የሰጠነው ብለዋል፡፡ ትምህርታዊ ጉብኝቱ በተለያዩ ቦታዎች የሚቀጥል ይሆናል።
ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጠቀሙ
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/tticommunication
ቴሌግራም፡https://t.me/tticommunication
http://tiktok.com/@ftti_official See less