ፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት
Federal Tourism Training Institute
We Strive for Excellence

ኢንስቲትዩቱ ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡

April 27, 2026
ኢንስቲትዩቱ ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ   ጋር   የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡

ሚያዝያ 2018 ዓ.ምየፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡የኢንስቲትዩቱ የጥናትና ምርምር ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ይታሰብ ስዩም ኢንስቲትዩቱ እና ዩንቨርሲቲው አብረው ሲሰሩ እንደነበር አስታውሰው
በቱሪዝም እና በሆቴል ዘርፍ በስልጠና በጥናትና ምርምር እና የማማከር አገልግሎት የሚሰጥ አንጋፋ ተቋም መሆኑን እና
ከዩኒቨርሲቲው ጋር የተደረገው ስምምነት የተቋሙን ተልዕኮ በማከናወን ሂደት አይነተኛ ሚና እንደሚጫወት ገልጸዋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር መንገሻ በበኩላቸው የአማራ ክልልና በተለይም ባሕር ዳር ከተማና አካባቢው ያለውን እምቅ የቱሪዝም ሀብት በአግባቡ ለማልማትና ለመጠቀም ይህ ስምምነት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ገልጸው ፣ ለትግበራውም ዩኒቨርሲቲው ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ፊርማውን የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ይታሰብ ስዩምና የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር መንገሻ አየነ ፈርመውታል።
ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጠቀሙ
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/tticommunication
ቴሌግራም ፡https://t.me/tticommunication
http://tiktok.com/@ftti_official