አካታችነትን ያከበረ፤ ለስኬት የበቃ፤ ሐምሌ 13/2018 ዓ.ም
የሆስፒታሊቲ ኢንደስትሪው ለአካል ጉዳተኝነት ቦታ አልነበረውም ይልቁንም ቁመት፣ ውብት ቅድሚያ ይሰጣቸው ነበር፤ በዚህ የተነሳ ብዙዎች ከዚህ ኢንደስትሪ ተገልለው ይኖሩ እንደነበር ይነገራል፡፡
በፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ይህን አመለካከት የሰበረ አካታችነትን ያከበረ እና ለስኬት የበቃ ሥራ እውን ሆነ፡፡
ወ/ሮ መስታዎት ጌታቸው ከጊዜ በኋላ በገጠማት ችግር የአካል ጉዳተኛ ሆናለች፤ ነገር ግን በአዲስ መንፈስ ራሷን አጠንክራ በቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት በቅዳሜና የእሁድ ( የእረፍት ቀናት) መርሃ ግብር በሆቴል ማኔጅመንት ትምህርቷን ተከታትላ ለመመረቅ በቅታለች፡፡
በትምህርት ጊዜዋ ምቹ ሁኔታዎች በማይኖሩበት ጊዜ መምህራኑ እና የትምህርት አስተዳደሩ ድጋፍ እያደረጉላት ስልጠናዋን ማጠናቀቋን ገልጻለች፡፡
የሆስፒታሊቲ ኢንደስትሪው ለሁሉም ክፍት መሆኑን እና ሙያውን ይዘው በዘርፉ የሥራ እድል ተጠቃሚ መሆን ለሚፈልጉ አካል ጉዳተኞች ሁሉ ማሳያ የሆነችውን መስታዎትን እንኳን ደስ አለሽ ማለት እንወዳለን፡፡
ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጠቀሙ
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/tticommunication
ቴሌግራም ፡https://t.me/tticommunication
http://tiktok.com/@ftti_official See less