ዓለም አቀፍ የአስጎብኚዎች ቀን “የሙያ ጉዞ ተግዳሮት እና ነገ በሚል የፓናል ውይይት ተከበረ።

ቱማኢ የካቲት 17/2018 ዓ ምቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ቱሪስት አስጎብኚ ባለሙያዎች ማህበር ጋር በመተባበር የዓለም አስጎብኚዎች ቀንን “የኢትዮጵያ የአስጎብኚ ባለሙያዎች የሙያ ጉዞ ተግዳሮት እና ነገ” በሚል ርዕስ የፓናል ውይይት አድርጓል። በፕሮግራሙ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ይታሰብ ስዩም እንደገለጹት አስጎብኚዎች ስለሚያስጎበኙት መዳረሻ በቂ መረጃና እውቀት እንዲሁም እውነት ላይ የተመሰረተ መረጃ…

Read More

የኢንስቲትዩቱ የሥራ ኃላፊዎች ባቡል ኸይር በጎ አድራጎት ድርጀትን ጎበኙ

ቱ ማ ኢ የካቲት 17/2018 ዓ ም ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ጥናትና ምርምር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ይታሰብ ስዩም እና ሌሎች የሥራ ክፍል ኃላፊዎች በባቡል ኸይር በጎ አድራጎት ድርጅት ጉብኝት አድርገዋል።የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት የጥናትና ምርምር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ይታሰብ በድርጅቱ የሚሰሩ ሥራዎችን በተግባር በማየት ቀጣይ ተቋሙን በስልጠና እና በተለያዩ ማህበረሰብ አቀፍ ተግባራት እንደሚደግፉ…

Read More

ቋሚ ኮሚቴው ከኢንስቲትዩቱ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት አደረገ።

የካቲት14/2018 ዓ.ም ቱማኢ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት አድርጓል። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ክቡር አቶ ጌታቸው ነጋሽ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ የተቋሙ የ6 ወር እቅድ አፈጻጸም በክቡር አቶ ገዛኸኝ አባተ፣

Read More

የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት እና ሀዋሳ ዩንቨርሲቲ በጋራ ለመስራት ተፈራረሙ።

የካቲት 13/2018 ዓ.ም ቱማኢ የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ከሀዋሳ ዩንቨርሲቲ ጋር በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ በተናጠል ያላቸውን ልምድና እውቀት ተጠቅመው በጋራ መስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የኢንስቲትዩቱ ም/ዋና ዳይሬክተር እና የምርምር፣ማማከር ዘርፍ ኃላፊ አቶ ይታሰብ ስዩም እና የሀዋሳ ዩንቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ ፈርመዋል።

Read More

ለኢንስቲትዩቱ ሠራተኞች የሥራ ላይ ስነ ምግባር ዙሪያ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እና በተቋሙ የተሠሩ ሥራዎች ቀረቡ ።

ቱማኢ ጥር/24/2018 ዓ ምቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ለአመራሮችና ሠራተኞች በሥራ ላይ ስነምግባር ዙሪያ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ።የተቋሙ ስነምግባር መከታተያ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ብርሃኑ ኩምሳ የሥራ ላይ ስነምግባር የተፈቀደ፣ የተወደደ፣ ያማረ ሥራ ወይም ድርጊት ማለት መሆኑን እና የሥራ ላይ ስነምግባር

Read More

የኢንስቲትዩቱ የሪፎርም ሥራዎች ተገመገሙ

ቱ.ማ.ኢ ጥር 23/2018 ዓ.ም የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት የሪፎርምና ISO 21001 2018 ያለበት የተግባር ምዕራፍ ግምገማ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል ። በውይይቱ ሁሉም የሥራ ክፍሎች የሪፎርምና የISO 21001 2018 አተገባበር ቀጣይነትን ይዞ ከመሄድ አኳያ ያሉበት ደረጃ በሱፐርቪዥን ቡድን ተፈትሿል። ውጤትም ከፍተኛ፣መካከለኛ እና ዝቅተኛ የሚል ደረጃ የተሰጠ ሲሆን ከሱፐርቪዥን ቡድኑ ምልከታ በኋላ በርካታ ሥራዎች መሻሻል እንደታየባቸው ተገልጿል።…

Read More

የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ የሚሸከም ባለሙያ መፍጠር የሚያስችል ፖሊሲ ተዘጋጅቷል ተባለ።

ቱ ማ ኢ ጥር/23/2018 ዓ ም ለቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት አሰልጣኞችና ባለሙያዎች የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ፖሊሲ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። ሰነዱን ያቀረቡት በሥራና ክህሎት ሚንስቴር የሚኒስትር ዴኤታ አማካሪ ዶ/ር ተሾመ ለማ ናቸው።

Read More

የኢንስቲትዩቱ የ2018 ዓ ም ግማሽ ዓመት የአፈፃፀም ሪፖርት ለሠራተኞች ቀረበ።

ቱ.ማ .ኢ ጥር 23/2018 ዓ ም በዚህ ፕሮግራም የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ነጋሽ እንደገለጹት ጥራት ያለው ስልጠና ምርምርና ማማከር የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲኖር የተሰሩ ሥራዎችን እየገመገምን ሁሉም የተሰጠውን ተልዕኮ መወጣቱን ለማየት ነው ብለዋል።አቶ ጌታቸው አክለውም የጋራ የሚያደርጉንን ምርኩዞች በመያዝና ቀጣይ ለምንሰራቸው ሥራዎች ዝግጁ የምንሆንበት የተለያዩ ስልጠናዎች እንደሚኖሩ ገልጸው በዚህ የምክክር መድረክ ሠራተኞች…

Read More

ሪፎርሙን በተዋረድ ባሉ መዋቅሮች ሙሉ በሙሉ ወደ ትግበራ ለማስገባት በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ

በሥራና ክህሎት ዘርፍ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን በተዋረድ ባሉ መዋቅሮች ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ያለመ የምክክር እና የአቅም ግንባታ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል። በመድረኩ የክልል ምክትል ቢሮ ኃላፊዎች ጨምሮ የሪፎርም አስተግባሪ ኮሚቴ አባላት በመሳተፍ ላይ ናቸው፡፡የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር እና የሚኒስቴሩ የሪፎርም ትግበራ አስተባባሪ አቶ ጌታቸው ነጋሽ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በበጀት ዓመቱ ሪፎርሙን ሙሉ ለሙሉ ወደ…

Read More

የዓለም ባንክ ግዥ ሥርዓት እና ኤሌትሮኒክስ ግዥን በተመለከተ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ ።

ቱ ማ ኢ ጥር 15/2018 ዓ ምበቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ከዓለም ባንክ ድጋፍ EASTIRP ፕሮጀክት ግዥ ሥርዓቱ ወደ ኤሌክትሮኒክስ በመቀየሩ ሥራው ለሚመለከታቸው ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ነው።ስልጠናውን የከፈቱት የተቋሙ የሥራ አመራርና አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ አባተ እንደገለፁት ከዚህ በፊት የነበረውን የግዥ ሥራ ጫና የሚቀንስና የጊዜና ጉልበት ቆጣቢ የሆነውን ሲስተም ሥራው የሚመለከታቸው ባለሙያዎች…

Read More