ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት በ20ኛው ግራንድ አፍሪካ የአመራርና የተቋማት ሽልማት ተሸላሚ ሆነ። ‎ግራንድ የአፍሪካ የተቋማት እና የአመራር ሽልማት ድርጅት፣ በኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ የልማት መስኮች የላቀ አፈፃፀም ላሳዩ ተቋማትና አመራሮች እውቅና በሚሰጥበት 20ኛው የሽልማት መርሃ-ግብር ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ቱሪዝም ዘርፍ ላለፉት 57ዓመታት ለነበረው አበርክቶ ድርጅቱ የራሱን ባለሙያዎች ልኮ አስጠንቶ እንዲሁም ባወጣው ጥብቅ መስፈርት መሠረት ተመዝን የዳይመንድ ደረጃ ተሸላሚ ሆኗል፤ትጉሆችንምአመስግኗል።ሽልማቱ‎ተቋማትና አመራሮች በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ተቀባይነት እንዲኖራቸው ማድረግ፣ጥራት ያለው ምርትና አገልግሎት እንዲቀርብ ማበረታታት ዓላማ ያደረገ የእውቅና መርሀ ግብር መሆኑ ተገልጿል።
‎ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጠቀሙ ፌስቡክ፡
https://www.facebook.com/tticommunication
ቴሌግራም ፡https://t.me/tticommunication
ዌብሳይት፡ https://www.tti.edu.et